Thursday, October 31, 2013

ህወሓትና ሙሴ ፡ ደርግና ሂትለር





በወርሐ ጉንበት 2005 ዓ.ም በአንድ ካፌ ውስጥ ቁጭ ብየ ሻይ ቡና በማለት ላይ ነበርኩ፡፡አንድ በ40ዎቹ መጨረሻና በ50ዎቹ መጅርያ የዕድሜ ክልል የሚገኝ ጎልማሳ እኔ በተቀመጥኩበት ጠረጴዛ የነበረው ክፍት ወንበር ሰው ይንሮው አይንሮው ካጣራ በኋላ መጥቶ ተቀመጠ፡፡በካፌው ውስጥ የነበረው ቴሌቪዥን ደርግ የወደቀበት የጉንበት 20 በዓል ዝግጅቶች በማሳየት ላይ ነበር፡፡የቴሌቪዥኑ ዝግጅት ከአጠገቤ ለተቀመጠው ሰውየ የሚመች አልነበረም መሰለኝ ‹‹ጉንበት 20 እኮ የህወሓት ድል እንጂ የኢትዮጵያውያን አይደለም›› እያለ ማጉረምረም ጀመረ፡፡‹‹የሃገራችን አንድነት የተናጋው ደርግ ተሸንፎ ህወሓት ለስልጣን ስለበቃ ነው፤ የህወሓት ዓላማ ስልጣን ብቻ ነበር…›› እያለ ያነበንባል፤ ባልመልስለተም እኔን ማናገሩ ነበር፡፡

እኔ በሐሳብ ማዕበል እንገላታለሁ፤አወርዳለሁ እወጣለሁ፤እየወደቅሁ እነሳለሁ፡፡በሓሳብ መርከብ ተሳፍሬ ሁሉንም ስፍራዎች አዳርሳለሁ፤ቆላውና ደጋው፣ገጠርና ከተማው፣ቅርብና ሩቁ አካልላለሁ… እማልደርስበት የለም፡፡አልፎ አልፎ እንዲህ ያደርገኛል፤አመል ሳይሆንብኝ አልቀረም፡፡አጠገቤ የተቀመጠው ጎልማሳ ብስልና ጥሬውን ይዘባርቃል፤በተመስጦ የምከታተለው ሳይመስለው አልቀረም፡፡ለተወሰነ ጊዜ መልስ ላለመስጠት ሞክሬ ነበር፤የኋላ ኋላ ግን አልቻልኩም፡፡ሰውየው የዋዛ አልነበረምና ኮርኩሮ ኮርኩሮ ሊያናግረኝ ችሏል፡፡የደርግ ሐጥያቶች እንዳለ በህወሓት ላይ መለጠፉን ሲቀጥል፣‹‹ ማስረጃህ ምንድንው?›› ብየ ጠየቅኩት፡፡‹‹እኔ እኮ ያኔ ትልቅ ነበርኩ፤አንተን በብዙ ዓመታት እበልጥሃለሁ፤ እንዳውም ሳልወልድህ አልቀርም፤እንዴት እንዲህ ትላለህ?›› እያለ የተናገረውን ሁሉ አሜን ብየ እንድቀበልለት ወተወተኝ፡፡‹‹አይ፣ በዕደሜ ብትበልጠኝም ብዙ የታሪክ ፅሑፎች ስላሉ በመረጃ አስደግፈን በንናገር ይሻላል ብየ ነው፡፡›› ስለው፣ ‹‹በለ ያዝ እንግዲህ፤ መረጃዎቹን ልዘርዝርልህ›› አለና፡

  1.  ደርግ ወደ ጦርነት የገባው በህወሓትና በሻዕብያ ተገድዶ እንደሆነ 
  2. የሰላምና የአብዮት ጥሪ አልቀበልም ብለው አሻፈረኝ በማለታቸው መሆኑን
  3. ደርግ ስልጣን የተረከበው መስከረም 1967 ዓ.ም ሲሆን ወያኔዎች ደግሞ ከሻዕብያ ጋር ወግነው በየካቲት 11 ቀን 1967 ዓ.ም(ደርግ ስልጣን ከያዘ ስድስት ወር እንኳን ሳይሞላው) በኢትዮጵያና ህዝቦችዋ ላይ ጦርነት በማወጃቸው ደርግ የሃገሩ ሰላምና አንድነት ለማስጠበቅ ወደ ውግያ መግባቱን ወዘተረፈ እያለ ሊያሳምነኝ ሞከረ፡፡ 



እኔም መረጃዎችን እያጣቀስኩ እሱ የሚላቸው ነገሮች በመክንያትና በመረጃ ያልተደገፉ የአስተሳሰብ ህፀፆች መሆናቸውን ላሳምነው ሞክርኩ፡፡ሰውየው ቀድሞውንም ለውይይት ሳይሆን ለወሃ ቀጠነ ክርክር የተዘጋጀ ነበርና ክርክራችን እየጋለ ሂዶ በሁለታችን በኩል መደማመጥ ጠፋ፡፡ከዛም በአነጋገር ዘየየ ትግራዋይነትየን ስላወቀ ነው መሰለኝ ‹‹ ድሮውም ከእናንተ ጋር መነጋገር ትርፉ ይህነው፤ሰው ሲናገር አትሰሙም፤ እናንተ ያለችሁት ግን ያለምንም ማገራገር እንዲሰማላችሁ ትፈልጋላችሁ…›› በማለት ራሱ የጀመረው ዝርጠጣ አርእስቱን ስለቀየረው ሂሳቤን ከፍየ ካፌውን ትቼለት ወጣሁ፡፡
ከላይ ያቀረብኩት ፅሑፍ ዓምና የተከሰተ ነበር፡፡ዛሬም ድረስ ግን ‹‹የደርግ ጭቆናዎች፣የዘር ማጥፋት ወንጀሎች፣ያለ ፍርድ የተፈፀሙ የንፁኃን ጅምላ ግድያዎች፣ቀይሽብር፣ የአውሮፕላን ድብደባዎች ወዘተ በህወሓት ምክንያት የተፈፀሙ ናቸው›› የሚሉ ወገኖች በጣም ብዙ ናቸው፡፡ብዙ ዋልጌዎች፣‹‹ደርግ ቀይ ሽብር ያወጀው ኢህአፓ ነጭ ሽብር በመጀመሩ ነው›› ብለው ይከራከራሉ፡፡ነገር ግን እነዚህ አባባሎች በህፀፆች የታጨቁ ሸውራራ አመለካከት የወለዳቸው ናቸው፡፡ከሰኔ 21 ቀን 1966 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1983 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ የተከሰቱት መልካአ ምድራዊ፣ማህበራዊና ምጣኔ ሃብታዊ ቀውሶች በደርጋውያን የተፈፀሙ ናቸው፡፡
የዚህ ፅሑፍ መነሻ ከላይ የተጠቀሱት ምክንያቶች ሲሆኑ ዓላማውም ድርግ ሃገር ያላሳደገው፣ተውልድ የገደለውና ሃገራችንን የጦርነት አውድማ ያደረገው ወዶ ሳይሆን ተገድዶ ነው የሚባለው አስተሳሰብ መሰረት የሌለውና የደርግ ጭካኔና ፈላጭቆራጭነት ለማድበስበስ የለመ መሆኑን በማስረጃ በማስደገፍ ፉርሽ ማድረግ ነው፡፡ደርግ ዓለም የመሰከረለት አምባገነን ነበር፤ የቄሳርን ለቄሳር ይሰጥ ዘንድ ግድ ነው፡፡

ህወሓት ለምን የትጥቅ ትግል መረጠ?


በኮለኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የተፃፈው ‹‹ትግላችን›› የተሰኘው መፅሓፍ እንደሚጠቁመው ደርግ የተረገዘው ከሰኔ 19 ቀን 1966 ዓ.ም ጀምሮ ነው፡፡በገፅ 153 ላይ ፣‹‹ከሰኔ 19 ቀን 1966 ዓ.ም ጀምሮ በአራተኛ እግረኛ ክፍለጦር ስብሰባ አዳራሽ በአዲስ አበባ ከተማና በአከባቢው የሚገኙ የጦር ክፍል ተወካዮች በተሰበሰቡበት ጊዜ…›› ይላል፡፡
ትንሽ ወረድ ብሎ በገፅ 157 ደግሞ፣‹‹ድርጅታዊ ሥራችንንና ምርጫችንን አከናውነን ሰኔ 21 ቀን 1966 ዓ.ም በቀኑ የሃገሪቱ የዜና ማሰራጫ ሰዓት በራድዮ፣እንዲሁም በምሽቱ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ገፃችንንና የተሰበሰብንበትን ስፍራ የሚያሳይ ቋሚ ወይም ተንቀሳቃሽ ስእላዊ መግለጫ ሳይታከል አጠር ባለ አጃቢ መግለጫ የደርጉን ህልውና ለኢትዮጵያ ህዝብ አበሰርን፡፡›› በማለት ድርግ በይፋ የተመሰረተበትና ዘውዳዊው አገዛዝ ወሽመጡ የተመታበት ቀን ይነግረናል፡፡ከዛች ቀን ጀምሮ የአፃው ስራዓት እየፈራረሰ የደርግ ስልጣን ደግሞ እየጠነከረ ቀጥሏል፡፡በዛች ቀን አምሳለ ሂትለሩ ደርግ በይፋ ተወልዷል፡፡የደርግ ልደት ግን ኮ/ሌ መንግስቱ ‹‹ለኢትዮጵያ ህዝብ አበሰርን›› እንዳለው ለኢትዮጵያ ህዝብ ብስራት ሳይሆን ታላቅ መርዶ ነበር፡፡
በመቀጠልም ደርግ ሽዋሚና ሻሪ እየሆነ መምጣቱን በገፅ 176 ላይ፣‹‹ጠቅላይ ሚኒስተር እንዳልካቸው መኮንን… ሊያጠፉን ስለሞኮሩ ሓምሌ 15 ቀን 1966 ዓ.ም ከሥልጣናቸው ወረደው ከመሰሎቻቸው… ጋር ተቀላቀሉ፡፡››በማለት ያስረግጥልናል፡፡‹‹ከመሰሎቻቸው ጋር ተቀላቀሉ›› ማለት ከ60ዎቹ ጋር ታሰሩ ማለት ነው፡፡ስለሆነም ሐምሌ 15 ቀን 1966 ዓ.ም ደርግ መሾምና መሻር እንዲሁም እንደፈለገው ማሰር የጀመረበት ቀን መሆኑን መታወቅ አለበት፡፡ጃንሆይ ግን ‹‹ንጉስ አይከሰስ፣ሰማይ አይታረስ›› የሚባለው ከእርሳቸው ጋር እኩል ያረጀው አባባል ተንተርሰው በማንቀላፋት ላይ ነበሩ፡፡ዳሩ ግን ግዛታቸውም በጥይት ታርሳለች፤እርሳቸውም መከሰስ ብቻም ሳይሆን ግድያም ተፈፅሞባቸዋል፡፡
ፕሮፌሰር ባሕሩ ከላይ በተጠቀሰው መፅሐፋቸው ላይ የ66ቱ አብዮት ጠንሳሾች የደርግ አካሄድ ምን ሊመስል እንደሚችል የታገሩት ትንቢት እንዲህ ፅፈዋል፤‹‹ ንጉሠ ነገሥቱ ከዙፋን ከመውረዱ ከሁለት ቀናት በፊት የወጣው ‹የሠፊው ሕዝብ ድምፅ› በወታደር የሚመራ መንግሥት፣ የፈለገውን ያህል ቅን ልቦና ቢኖረው፣ ዞሮ ዞሮ አገሪቷን ባንድ አምባገነን መሪ መዳፍ ሥር ይጥላታል ሲል ትንቢታዊ ትንተና አቅርቦ ነበር፡፡››(ገፅ 247)
መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም ዘውዳዊው ስርዓት ተገርስሶ በወታደራዊው አምባገነን መተካቱን የኢትዮጵያ ህዝብ መርዶ ሰማ፡፡ከዛም የደርግ አዋጆች መጉረፍ ቀጠሉ፡፡መስከረ 4 ቀን 1967 ዓ.ም ከአራት ኪሎ ግቢ የተጀመረው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሰላማዊ ስልፍ በደርግ ወታደሮች ተቋርጠዋል፡፡የተቃውሞ ሰልፉ ተከትሎም በሰላማዊ ሰልፊ የሚደረግ ተቃውሞ የሚያግድ የአደጋ ጊዜ አዋጅ በደርግ ታወጀ…
የህይወት ተፈራ ‹‹Tower in the sky›› የሚከተለውን ያስነብበናል፡

… On 16 September, 1974 University students organized a demonstration that commenced from Arat Kilo campus. It was going to be the litmus test for the Derg’s patience.
… All of a sudden, we heard shots when we reached Berhanena Selam Printing press in Arat Kilo. There was total chaos…

… A few days after the protest rally, the Derg declared a state of emergency prohibiting protest demonstrations and strikes. It held union leaders and members of the armed forces in custody, accusing them of calling out for Provisional Peoples’ Government, and killed peasants in different provinces for demanding land. In October, it threw teachers and others into jail, on charges of pushing for a Provisional Peoples’ Government. Five members of the armed forces were killed, and several wounded in Harar. A number of people standing in front of the office of the workers’ union looking for a job were mercilessly shot dead.
The Derg’s motto, Ethiopia Tikdem yaleminim dem – Ethiopia first without blookshed – became tainted with blood. (ገፅ 114-116)

ሃይላይ ሓድጉ በ‹‹ፅንዓት›› መፅሐፉ እንዳሰፈረው፣ ደርግ ሕዳር 12 ቀን 1967 ዓ.ም
ማንኛውም ሰው ‹ኢትዮጵያ ትቅደም› የሚለውን ዓላማ ለመፈፀም በመንግስት ወይም በመንግስት በለስልጣን የሚወጡ አዋጆች፣ድንጋጌዎች፣ትእዛዞች እና ደሞቦች እንደይከበሩ፣በንግግር፣በፅሑፍ ወይም በማንኛውም መንገድ በግልፅ ሲያነሳሳና ሲያደፋፈር ከተገኘ ከአንድ እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ከባድ የእስር ቅጣት ይቀጣል፡፡(ገፅ 37)
 የሚል አዋጅ አውጥቶ ማንኛውም ሰላማዊ ተቃውሞ ተቀባይነት እንደሌለው አሳወቀ1፡፡

Sunday, October 27, 2013

ንፋስ ዓድና፡ ቅደምን ሎምን




ወዲ ክንደይ ዓመት ከምዝነበርኩ ብዕሊ ኣይዝክሮን፤ግን ቡዙሕ ዓመታት ኣቑፂሩ ኣሎ፡፡ ከምዝ ሎሚ ብሓይሊ ፀሓይ ዝሰርሓ ባትርታት ናብ ገጠራት ትግራይ ቅድሚ ምትእትታወን፣ ፀሓይ ዓሪባ ምድሪ እንትፅልምት እታ ላምባ ዝመልአት ኩራዝ ክትውላዕ ግድን እዩ ነይሩ፡፡መይዳ እንደርታን ካብ ዓዲ ሽሁ ሒዝካ ክሳብ ማይጨው ዘሎ ደጉዓ ራያን ንፋስ ሃም ልብኻ እዩ እሞ እታ ንፅሓ ተኪኣ ብርሃን ትህብ ዝነበረት ኩራዝ ጊብ ኣቢሉ የጥፍኣ ነይሩ፡፡
ሽዓኡ፣ ኣዴታትና ‹‹ኤህ! እዝ ንፋስ እዚ ዶ! ድርግም የብሎዋ፤ድርግም እኮ ኣቢሉዋ!ኣታ እቲ ማዕፆ እስቲ ዕፀዎ፡፡›› ይብላና ነይረን፤ በቲ ሃንደበታዊ ፀልማት ምዓንጣአን ሕርር እናበለ፡፡ኣብ ገጠራት ትግራይ ዝነብራ ኣዴታትና፣ ገራሁ እንትሕረሱን ባዝርእቲ እንትሽፈኑን ምባሮ ሒዘን ይባሩዋና ይጉልጉላን፡፡እቲ ዝትዘረአ እኽሊ ዓወል ውሒጥዎ ከይተርፍ ምስ ኣስኡነን ሓቢረን ይፅህይያ፡፡ኣብ እዋን ቀውዒ ከዓ ኣብ ዓፅዳን ኮልሳስን መቀነተን ሸጥ ኣቢለን እናተፃፈዓ ይውዕላ፡፡ናይ ኣዴታት ገጠር ስራሕ ግን ፅሓይ ምስዓረበት እውን ቐፃሊ እዩ፤ ኣብ ዝዋዓላ ውዒለን፣ ብዓል ገዘአንን ደቀን ንምዕንጋል ደፋእፋእ ይብላ፡፡ስለዝኾነ ድማ እየን ነታ ብርሃን ትልግስ ዝነበረት ኩራዝ ወይከዓ ሽምዓ ንፋስ ከጥፋኣ ከሎ ‹‹ኤህ!›› ኢለን ክረግምኦ ዝግደዳ ዝነበራ፡፡
ንፋስ ብጣዕሚ ፈጣን ንዝኾነ ነገር ንምግላፅ ኢና ንጥቀመሉ ነይርና፡፡ ብፍጥነቱ ንዝፍለጥ ተሓሪሱ ዘይፀግብ ብዕራይ ‹‹ጭለይ ብዕራይና እኮ ንፋስ እዩ፡፡›› ንብሎ፡፡ጎይዮም ዘይቅደሙ ወይ ከዓ ዘይስዓቡ ነገራት እውን ‹‹ንፋስ›› ዝብል ቅፅል ይውሃቦም፡፡ዕሸል እናሃለኹ ‹‹ ወዲ ንፋስ›› እናበለና እንፅውዖ ቆልዓ ከም ዝነበረ ይዝክር፡፡ወዲ ንፋስ ቀጢን ነዊሕ እንትኾን ‹‹ብጉያ ዝወዳደሮ ኣይነበረን›› ይብሃል፡፡
ዝብኢ ርኢኹም ዝትፈልጡ ሰባት ሓንቲ እግሩ ሓፃር ስለዝኾነት ‹‹ጎሰስ…ጎሰስ…ሾኽለል…ሾኽለል›› እናበለ ከም ዝኸይድ ከይተዓዘብኹም ኣይትተርፉን፡፡እዚ ዝኾነሉ ምኽንያት፣ ዝብኢ ‹‹ንንፋስ ክቕድሞ እየ›› ኢሉ ስለዝፈከረ ምስ ንፋስ እንተወዳደር እግሩ ከም ዝተሰበረ ዝትሕብር ፅውፅዋይ ኣላ፡፡ህፃን እናሃለኹ፣ ጎይዩ ንንፋስ ዝቐድም ነገር ከም ዘየለ ይሰምዕ ነይረ፡፡
ንፋስ ብዘይካ ጉልበትን ፍጥነትን ጥበብ ከም ዘይብሉ ይንገር፡፡ቅደም…ቅደም…ቅደም… እምኒ ሕምባሻ እናሃለው ከይኾነ ኣይተርፍን፣ ንፋስን ፅሓይን ትወራሪዶም ይብሉዋቶም፡፡ሓደ ሰልዐም መንእሰይ ኩታኡ ትጎፊኑ፣ በትሩ ኣብ ማእገሩ ገይሩ ናብ ጣጣኡ እንትጉዓዝ ዝተመልከቱ ንፋስን ፅሓይን ናይቲ ስብኣይ ኩታን ጃኬትን ብሓደ ግዜ ንምሕዳግ እዮም ትወራሪዶም፡፡
ንፋስ ብሃንደበት ዘሎን ዘየሎን ሓሉ ተጠቒሙ ብምንፋስ ንትስብኣይ ጥራሑ ከውፅኦ እንትሙክር፣ ስብኣይ መሬት ሒዙ ለጥ ይብል እሞ ወዮ ንፋስ ፈኪሩ ይተርፍ፡፡ፅሓይ ከዓ ‹‹በል ትመልከት›› ትብል እሞ ስራሓ ትጅምር፡፡እቲ ስብኣይ እንትጉዓዝ ንሳ አውን ሙቐታ ኣበርተዐትሉ፡፡ስብኣይ ኣይክኣለን፤ ኩታኡ ዓፃፂፉ ኣብ ማእገሩ ብምግባር መንገዱ ይቕፅል፡፡ሐዚ እውን እታ ፅሓይ ሙቐታ ብምውሳኽ ነቲ መንገደኛ ርሃፅ ብርሃፅ ስለዝገበረቶ ጃኬቱ ኣውፂኡ ኣብ ኩርናዑ ብምግባር ጉዕዞኡ ይቕፅል፡፡ብምዃኑ ድማ ፅሓይ ኣሸናፊት ትኸውን፡
ኣብ መፅሓፍ ቅዱስ ትደጋጊሞም ዝተጠቐሱ ኣርባዕተ ንፋሳት ኣብ ግዜ ምፅኣት ዝልኣኹ እዮም፡፡ንኣብነት፣ኣብ ትንቢተ ዳኒኤል ምዕራፍ ሸውዓተ ካብ ቁፅሪ ሓደ ጀምሩ ዘሎ ራኢ ኣርባዕተ ንፋሳት ካብ ባሕሪ ብምንፋስ ኣርባዕተ ዝተፈላለዩ በላዕቲ ነፍሳት ሒዞም እንትመፅኡ የንብበና፡፡እቶም በላዕቲ ነፍሳት ድማ ናይ ኣርባዕተ ውልቀ መለኽቲ ንጉሳት ምንጋስ ከም ዝትንብዩ ይነግረና፡፡
ንፋስ ቀውዒ ንሓረስታይ ወሳኒ ተፈጥራዊ ሓይሊ እዩ፡፡እኽሊ ካብ ሓሰር ንምፍላይ ኣዝዩ ጠቓሚ እንትኸውን ‹‹ጎሪባ›› ተባሂሉ ይፅዋዕ፤ ምንእንታን ከይሕሰም ዝውሃቦ መፀወዒ እዩ፡፡
እቶም ኣብ ላዕላይ ዝገለፀኩዎም ባህርያታት ንፋስ ባህላዊ ኣታሓሳስባና ዝፈጠሮም ኣመላኻኽታታት እንትኾኑ ናይ ሎሚ ዘበን ንፋስ ግን ንጥፍኣት ጥራሕ ከይኾነስ ብዘመናዊ ኣሰራርሓ ኣብ ልምዓት ክውዕል ከም ዝኽእል ካብእቲ 120 ሜጋ ዋት ሓይሊ ኤሌትሪክ ናይ ምምንጫው ክእለት ዘለዎ ልምዓት ኣሸጎዳ ምርዳእ ይክኣል፡፡እቲ ካብ ቀላቅል ዓፋር ዝውርወር ንፋስ ኣሸጎዳ ልቺ ተወሊዓ ንምርኣይ ምብፃሕና ኣዐርዩ ዘሐብን እዩ፡፡
እወ፣ እቲ ቕደም ኩራዝ ወይ ድማ ሽምዓ ወሊዕና ድራር ኣብ እንበልዐሉ እዋን ሃንደበት ድርግም ኣቢሉ ብፀላም ለይቲ ንክንውረር ዝገብረና ዝነበረ ንፋስ ሎሚ ን24 ሰዓታት ሓይሊ መብራህቲ ንምሃብ ተዳሊዉ ይርከብ፡፡ምዝዛም ልምዓት ንፋስ ኣሸጎዳ ነቲ ብምቁርራፅ ሓይሊ መብራህቲ ዝሳቐ ዘነበረ ህዝብና ዓብይ ዓወት እዩ፡፡











Photo:fanabc.com

Sunday, October 20, 2013

ጭፍን ደጋፊዎች፣ ጭፍን ተቃዋሚዎች፣ ለዘብተኞችና ገለልተኞች በኢትዮጵያ




ጭፍን ደጋፊዎች


‹‹ከተፈጠረች ጀምሮ ፀሐይ የሚወጣባትን አገር ጭፍን ደጋፊዎች ‘ኢሕአዴግ ባይኖር ኖር ፀሐይ አትወጣም ነበር’ ይላሉ፡፡ መንግሥት ልማታዊ ስለሆነ ‘ኦክስጅን በሽበሽ ነው’ ይሉናል፡፡ የውጭ ምንዛሪ እጥረት እያለም ለነሱ በሽበሽ ነው፡፡ ቃላቶቻቸው ሁሉ ሁሌም ‘ተደነቀ ተሞገሰ’ ነው፡፡ ያለውን ተጨባጭ ችግርና ጉድለት እየገለጹ መንግሥትና ገዥው ፓርቲ እየታረሙ እንዲጠናከሩ ከማድረግ ይልቅ፣ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ እየሸፋፈኑና እየካዱ መንግሥትን ወደ ስህተትና ጥፋት ሲገፉት ይውላሉ፡፡››



የኢትዮጵያ ችግሮች፡- ድህነት፣የብሔር ብሔረሰቦች ብዛትና ልዩነት፣በተለያዩ ቋንቋዎች መፃፍና መናገር፣ሙስና፣የመልካም አስተዳደር እጦት፣ የዘርፍጅት መልካምነት የሚሰብኩ ጋዜጦችና  መዘጋትና የጋዜጠኝነት ስነ ምግባር የሚጥሱ ጋዜጠኞች መታሰር ወዘተ በገዢው ፓርቲ አማካኝነት የመጡና ለእርካሽ ፖለቲካ ሲባል የሚከናወኑ ናቸው፤ በጭፍን ተቃዋሚዎች እይታ፡፡በቃ፣ ኢህአዴግ ስልጣኑ በለቀቀ ማግስት ኢትዮጵያ ወደ ገነትነት ትቀየራለች ብለው ያስባሉ፡፡ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሚታሰረው ኢህአዴግን ስለሚቃወም ብቻ ነው ይሉናል፡፡የገቢዎችና የጉምሩክ ባለስልጣናት የታሰሩ ሰሞን ሲያስተጋቧቸው የነበሩ የፖቲካ ዙርያ ጥምጥሞች እንስታውስ፡፡
 



ጭፍን ተቃዋሚዎች


‹‹በሚያሳዝንና በሚዘገንን ሁኔታም በአገራችን ጭፍን ተቃውሞ እየተሰማ ነው፡፡ በኢትዮጵያ እየታየ ባለው ልማትና መነሳሳት አፍሪካውያን ራሳቸው ኢትዮጵያን እንደ ተምሳሌት እየወሰዱ ባሉበት ጊዜ፣ ጭፍን ተቃዋሚዎች ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገሮች ኋላ ቀረች ይሉናል፡፡ ከጥላቻና ጭፍን ተቃውሞ በመነሳት መንገዱ የውሸት ነው፣ ሆስፒታሉ የውሸት ነው፣ ትምህርት ቤቱ የውሸት ነው ይሉናል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢሕአዴግ ስለሆነ ኤሚሬትስ ይሻላችኋል፣ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አትብረሩ ይላሉ፡፡ በዓባይ ወንዝ ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ መገንባት የለበትም ይሉናል፡፡ ኢሳያስ አፈወርቂን የመሰለ ጀግና የለም ይላሉ፡፡ ከግብፅ አምስት መቶ ሺሕ ዶላር ተሰጠን እያሉ ይለፈልፋሉ፡፡ ኢሕአዴጎች ጤፍና እንጀራ ወደ ውጭ ስለሚልኩ እንጀራ አትብሉ፣ የጤፍ እንጀራ አትግዙ የሚሉ የተቃዋሚ ሬዲዮ ጣቢያዎችም ተደምጠዋል፡፡ ለዓለም ባንክ፣ ለአሜሪካና ለአውሮፓ ኢትዮጵያን አትርዱ፣ በኢትዮጵያ ኢንቨስት አታድርጉ የሚል ልመናና ተማፅኖ አድምጠናል፡፡ ››


ጭፍን ደጋፊዎችና ጭፍን ተቃዋሚዎችን የሚተቹ፣የገዢው ፓርቲና የተቃዋሚ ፓረቲዎች አፍራሽ ተግባራት ነቅሰው በማውጣት ከስህተቶቻቸው እንዲታረሙ የሚመክሩና የሚገስፁ ወገኖች ደግሞ የቡርኩታ ዕጣ ፈንታ እያጋጠማቸው ይገኛል፡፡ቡርኩታ የሚጠበሰው(የሚሰራው) በተድቦለቦለው የገብስ ቡኽእ ውስጥ እንደ ብረት ግሎ የቀላ የድንጋይ አለሎ ይጨመርበትና ተድቦልቡሎ ወደ እሳት ማገዶ ይገባል፡፡እናም ከውስጥም ከውጭም ይጠበሳል፡፡የሚዛናዊ ተቺዎች ዕጣም እንዲሁ ነው፡፡ የመንግስት ችግሮች ከነቀፉ ጭፍን ደጋፊዎች ይዘምቱባቸዋል፤ ከተቃዋሚው ጎራ እንደተሰለፉ አድርገው ይፈርጅዋቸዋል፡፡የተቃዋሚዎች አፍራሽ አካሄዶች ከዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎችና የታሪክ ክስተቶች ተመስርተው ሲተቹም እንዲሁ የጭፍን ተቃዋማች ሰለባ ይሆናሉ፤ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ናቸው ይባላሉ፡፡

በነዚህ ምክንያቶች አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ‹‹ፖለቲካና ኮረንት በሩቁ ነው›› የሚል አባባል በመተግበር ላይ ይገኛሉ፡፡ፖለቲካ ተንከፍ ውይይቶች በተነሱ ቁጥር ራሳቸው ገሸሽ ያደርጋሉ፤ ከማንኛውም ሃገራዊና ዓለም አቀፋዊ የፖለቲካ ሁነቶች ለመራቅ ሲሉ ይሞክራሉ፡፡የፖለቲካ ፅሑፎች በሩቁ የማግለል አዝማምያ ይታይባቸዋል፡፡ለዚህም ነው አብዛኞቹ የሃገራችን የተቃዋሚ ፓርቲዎች በአፄው ዘውዳዊ አገዛዝ አንቱ የተባሉ ቱባ ባለስልጣናት፣ የወታደራዊው አምባገነን አማካሪዎችና ‹‹አወንታዊ ተቺዎች›› በነበሩና ውሃ እንደነካው ሳሙና በሚምለጨለጭ ባህርያቸው አማካኝነት ከኢህአዴግ ጋርም ስልጣን ተጋርተው ህዝቡን እኩል ሲረግጡ ኖረው በ11ኛው ሰዓት ከስልጣን በተባረሩ እስስቶች እየተመሩ ያሉት፡፡ሁሉም ለማለት በሚቻል መልኩ የ60ዎቹ ነውጠኛ ትውልድ ውጤቶች ናቸው፤ በኢህአዴግም በተቃዋሚውም ጎራ ተሰልፈው ይህ ትውልድ እንዳሻቸው እያሽከረከሩት ያሉት፡፡መድርክና በመድርክ ስር የተሰባሰቡ ፓርቲዎች ለዚህ አባባል በግንባር ቀደም የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

ለምሳሌ ዓረናን እንውሰድ፤ በጳጉሜ የማእከላይ ኮምቴና የስራስፈፃሚ አባል ሆኖ የተመረጠው አብራሃ ደስታ ‹‹ ዓረና ከህወሓት ተገንጥለው በወጡ የድሮ ፖለቲከኞች ስለሚመራ ከህወሓት በምንም መልኩ አይለይምና በአዲስ ትውልድ ይምትለው ሊቀ ምንበራችሁ ሳይቀር የህወሓት አባል የነበረ አይደለም ወይ? በአዲስ ትውልድ ለምን አልተካችሁትም?›› ብየ ጠይቄው ነበር፡፡ህወሓት ያልነበረ በሳል መሪ ስላጣን ሲል ነበር የመለሰልኝ፡፡አውነታው ግን ዓረናን መምራት የሚችል በሳል መሪ ስለጠፋ ሳይሆን በፖለቲካ ውስጥ እጁ ለማስገባት የሚፈልግ የትግራይ ተወላጅ ስለጠፋ ነው፡፡እንጂ ብዙ እጅግ በጣም ብዙ ምሁራን አለ፤ ከተቃዋሚውም ከህወሓትም ጎራ ያልተሰለፉ፡፡

ለምን ቢባል ደግሞ ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርኩት ለዘብተኛና ሚዛናዊ የሆነ ፖለቲካ የሚያራምዱ ወገኖች የቡርኩታ ዕጣ ፈንታ ስለሚገጠማቸው ተስፋ ቆርጠው ራሳቸው ስለሚያገሉ ነው፡፡ይህ አካሄድ ግን በፖለቲካውም በምጣኔ ህብቱም የበለፀገች ኢትዮጵያ የማየት ህልማችን መና ሊያደርግ የሚችል ውጤት ስላለው ከወዲሁ መቅረት ያለበት ይመስለኛል፡፡ጭፍን ተቃዋሚዎችና ጭፍን ደጋፊዎች በአካል ተገናኝተው በሰለጠነ ውይይት ችግራቸውን ለመፍታት አይችሉም፡፡መሰዳደብ፣መፈራረጅ፣ጣት መቀሳሰር ነው የሚቀናቸው፡፡በሁለቱም ፅንፎች ያሉ ወገኖቻችን አንዱ ሌላኛውን ካለጠፋ በስተቀር አብረው መኖር የሚችሉ ዓይነት አይደሉም፡፡የ60ዎቹ አክራሪዎች ያስከተለው የነጭና የቀይ ሽብሮች እልቂት ምንጊዜም መርሳት የለብንም፡፡
እንዚያ አዝማምያዎች ዛሬም ድረስ አብረውን አሉ፤ ጭፍን ተቃዋሚዎች ገዢው ፓርቲ የፈለገው በጎ ነገር ይስራ የሚያጣጥሉበት መንገድ ይፈልጋሉ እንጂ እውቅና ለመስጠት ብቃቱም ወኔውም የላቸውም፡፡ኢያጎአዊ ‹‹ኢጎአቸው›› ጠፍሮ ይዞ አላላውስ አላንቀሳቅስ ብሏቸው ይገኛል፡፡ገዢው ፓርቲም ለሃገር ቅድሚያ በስጠት የግላቸው የስልጣን ጥማት ገሸሽ አድርገው ለዘብተኛ በሆነ መልኩ የሚቃወሙትን ከፅንፈኞቹ ጋር ሲፈርጃቸው ይታያል፡፡ሁለቱም ግን ለሃገራችን ቀጣይነት ስለማይበጁ በለዘብተኛውና አርቆ አሳቢው መተካት አለባቸው፡፡ይህ እውን የሚሆነው ደግሞ ‹‹ፖለቲካና ኮረንቲ ብሩቁ›› እያሉ በመሸሽ ሳይሆን የሃገር ጉዳይ መሆኑን አውቆ የመጣው ይምጣ፤ የተባለው ይባል ብሎ ቆርጦ በመነሳት ብቻ ነው፡፡ካልሆነ ግን እንደ ‹‹ኢነርት››ብረቶች የአሲዶች ማሸግያና መሸሸግያ እንዲሁም ማጓጓዣ ሆኖ መቅረት ነው፡፡

ግን እስከ መቸ ነው አብዛኛው ሰላማዊና ለዘብተኛው ወገን የጥቂት ፅንፈኞች መጫወቻ ሆኖ የሚኖረው?እነዚህ ፅንፈኞች(የፖቲካና የሃይማኖት) መነሻና መድረሻቸው የግል ጥቅማቸውን ማሳካት ብቻ ነው፡፡ለዛም ነው እነሱ ካሉትና ካከናወኑት በስተቀር የሌሎች አስተሳሰብና አስራር(ሃገራዊ ጥቅማቸው የተራጋገጡም ቢሆን) በጭፍን ሲቃወሙ የሚታየው፡፡በጭፍን መቃወምና መደግፍ እንዲሁም ‹‹ፖለቲካና ኮረንቲ ብሩቁ›› እያሉ ከሃገራዊ ጉዳዮች ራስን ማግለል መቆም አለባቸው፡፡



ደጋፊውም ተቃዋሚውም ሚዛን አልባ እየሆነ ነው:ethiopianreporter.com




Tuesday, October 15, 2013

የሰማያዊ ፓርቲ አማራጭ ህገ መንግስት አውን አማራጭ ነው?




ሃገራችን ኢትዮጵያ ለዘመናት በዘውዳዊ አገዛዝ ስትረገጥ ኖራለች፡፡የ60ዎቹ አብዮት በመጥለፍ ህዝቡን አንደ ብረት አቅልጦ እንደ ዱቄት ፈጭቶ ‹‹በኢትዮጵያ ትቅደም›› ስም የአንድ ትውልድ ወጣቶች በግፍ የጨፈጨፈውና ሃገሪቱ ወደማትወጣው ድህነት የከተተው ደርግም ዘውዳዊው አገዛዝ በወታደራዊ አምባገነናዊ አዛዝ ነበር የቀየረው፡፡ሃገራችን ከደርግ ያተረፈችው ነገር ቢኖር ድህነት ነው፤የልጆቿ ያለ ፍርድ መጨፍጨፍ ነው፤ ስርዓት አልባነት ነው፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ እነዚህን ተከትሎ የመጣው ‹‹ፖለቲካና ኮረንቲ በሩቁ›› የሚሉት አባዜ ነው፡፡
በንጉሱ አስተዳደር (ከዛ በፊት በነበሩ ኋላ ቀር ነገስታትም ጭምር) ብዙ አፍራሽ ነገሮች ተከስተዋል፡፡በፊውዳሉ የአገዛዝ ዘመን ኢትዮጵያን ‹‹አንድ ሃይማኖት፣ባህልና ቋንቋ ያላት አንዲት ብሔር›› ለማድረግ ሲባል ከ80 በላይ የሆኑ ብሔር ብሔረሰቦች በሃይል ሲደፈጠጡ ንሯል፡፡የባሌ፣የጎዣምና የትግራይ አርሶ አደሮች የመብት ጥያቄዎች የእንግሊዝ አውሮፕላኖች በሚያዘንቡት የቦምብ ናዳ ነበር መልስ የተሰጣቸው፡፡ የኤርትራ ፌደሬሽን ቀርቶ እንደ ሌሎቹ ጠቅላይ ግዛቶች የንጉሱ የግል ንብረት ለማድረግ በተደረገው የመብት መደፍጠጥ ኋላ ላይ እንድናጣት ምክንያት ሆኗል፡፡ የትግራይና ወሎ ጠቅላይ ግዛቶች ረሃብ በንጉሱ የ80ኛ በዓል ምክንያት ተረስተው ብዙ ህዝብ እንደ ቅጠል ረግፈዋል፡፡
በወታደራዊው የአገዛዝ ዘመን የዘውዳዊው ስርዓት ጨፍጫፎችና የመብት ረገጣዎች በሽዎች ተባዝተው ምሊዮኖች ህይወታቸውን አጥተውበታል፤ ሃገሪትዋም የድህነት የረሃብ ተምሳሌት እንድትሆን አድርጓታል፡፡የወሎና የትግራይ ድርቅ ብሶበታል፤ መፍትሔውም ህዝቡ በሃይ ቀየውን እንዲለቅ በማድረግ በየሰፈራ ጣብያው ረግፎ እንዲቀር ነበር ያደረጉት፡፡ንጉሱን ጨምሮ 60 ትላልቅ ባለስልጣኖች ያለ ምንም ፍርድ በመግደል ስልጣኑን የጀመረው የመንግስቱ ጭራቃዊ አገዛዝ ቀይ ሽብሩ ሲጋጋል በቀን እስከ 54 ሽህ ወጣቶች በመጨፍጨፍ ለተገደሉበት እያንዳንዱ ጥይት ወላጆቻቸው 120 ብር እንዲከፍሉ ተገድዷል፡፡በጎንደርና በትግራይ ‹‹አሳውን ለማጥፋት ባህሩን ማድረቅ›› በሚሉት ፍፁም እንስሳዊ አስተሳሰብ ህዝቡ በገበያ ቀኖች፣በክብረ በዓላትና ስርዓተ ቀብር በሚካሄድባቸው ጊዚያቶች በተደጋጋሚ በሚጎች ተደብደቧል፡፡
እነዚህ ሁሉ ግፎች ታሪክ ሆኖው ኢህአዴግ ደርግን ድባቅ በመምታት ስልጣን ሲጨብጥ የብሔር ብሔረ ሰቦችና ህዝቦች መብት የሚያስከብር ህገ መንግስት ተረቆ ሃገራችን በፌዴራላዊ ስርዓት ትስተዳደር ጀመር፡፡ህገ መንግስቱ የግለሰብ መብት ብቻ ሳይሆን ለዘመናት ተረግጠው የኖሩ የብዱን መብቶችም እንዲከበሩ በመፍቀዱ የተለያዩ ዓይነት ባህሎች፣ ቋንቋዎችና ልምዶች ማደግ ጀመረዋል፡፡ለምሳሌ ‹‹የትግራይ ህዝብ ታሪክ ይሰራል እንጂ ታሪክ አዘግብም›› የሚባለው አባባል ታሪክ ለመሆን የበቃው በቋንቋችን እንድንማር ስለተፈቀደልን ነው፡፡በአሁን ጊዜ የትግራይ ህዝብ ታሪክ በራሱ ተወላጆች በትግርኛ እየተፃፈ ይገኛል፡፡ ድሮ ግን አንድ አንድ የታሪክ ምሁራን ነን ባዮች በምርቃና የፃፉትን ነበር ስንማር የኖርነው፡፡ሌሎቹ ብሔሮችም እንዲሁ ባህላቸውና ታሪካቸው በራሳቸው ቋንቋ በመፃፍ ይገኛሉ፡፡
ይህ ለውጥ ግን በህዝቡ ክንድ ተቀጥቅጠው ከስልጣን ለተባረሩ የድሮ ስርዓት ርዝራዦች ራስ ምታት ሆኖባቸዋል፡፡የፌደራል ስርዓት መዋቅሩና የብሔር ብሔረሰቦች መብት መከበር የአንድ ትውልድ ዕድሜ(23) ያህል በመቆየቱ የሚይዙት የሚጨብጡት አሳጥቷቿል፡፡ከጥቂቶች በስተቀር የሁሉም ተቃዋሚዎች ለማለት በሚቻል መልኩ ዓላማቸው የድሮው ጨቋኝ ስርዓት ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ነው፡፡ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶች፣ የመብት እኩልነት፣የፕረስ ነፃነት ወዘተ እያሉ የሚለፍፉት የስልጣን ጥማቸውን እስኪያረኩ ነው እንጂ ስለነዚህ ነገሮች ተቆርቁረው አለመሆኑን አካሄዳቸውን በማጤን ብቻ ማወቅ ይቻላል፡፡አብዛኞቹ የፓርቲዎች አመራሮች ከሶስት ጊዜ በላይ ፓርቲዎች ቀያይሯል፤ እስካሁን ግን በአንዱም አልተሳካላቸውም፡፡የተቀሩት ደግሞ ሲመቻቸው ብረት አንስተን እንዋጋለን ይላሉ ካልተመቻቸውም በሰላማዊ መንገድ እንታገላለን በማለት የሚገለባበጡት ስለሃገርና ስለህዝቦቿ አስበው ሳይሆን የግል ጥቅማቸው የተነካባቸው መስሎ ስለሚሰማቸው ነው፡፡
ከእነዚህ የከሰሩ ፖለቲከኞች ስብስብ አንዱ የሆነው የግንፍሌው ሰማያዊ ፓርቲ ሲሆን ከመቶ በላይ አባላት ሳይኖሩት የኢትዮጵያ አማራጭ ህገ መንግስት ማርቀቁን አስታውቋል፡፡እንደ ሌሎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምክንያት ሳይሆን በጭፍን ጥላቻና በስሜታዊነት የሚንቀሳቀሰው የፓርቲው ስብስብ የፌዴራል ስርዓት አወቃቀሩ በአሀዳዊ ለመቀየር እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ይህ የሰማያዊ ፓርቲ ዓይነቱ ህገ መንግስት ግን አዲስ አይደለም፤ በደርግና በዘውዳዊው ስርዓቶች የነበረና የህዝብ ተቀባይነት አጥቶ የፈረሰ ነው፡፡

ከፌዴራላዊ የመንግሥት አወቃቀር ይልቅ አሀዳዊ የመንግሥት አወቃቀር?

ፌዴራላዊ የመንግስት አወቃቀር ብዙ ብሔር ብሔረ ሰቦችና ህዝቦች ባለት ሃገር የሚመረጥና አዋጪ መሆኑን የተረጋገጠ የመንግስት አወቃቀር ነው፡፡ከቻይና በስተቀር በጣም ሰፋፊና ብዙ ብሄር ብሔረ ሶቦች የሚኖሩባቸው ሃገሮች ፌዴራላዊ የመንግስት አወቃቀር ይከተላሉ፡፡አሜሪካ፣ራሽያ፣አውስትራልያ፣ብራዚል፣ህንድ ወዘተ የዚህ ዓይነት አወቃቀር ተከታዮች ናቸው፡፡በዚህ ምክንያት ነበር ሃገራችን ኢትዮጵያም የፌዴራል ስርዓት ተከታይ እንድትሆን የተወሰነው፡፡አሃዳዊ የምንግስት አወቃቀር ግን አንድ ብሔር (አናሳ ብሔሮች) በሚኖርባቸው ትናንሽ ሃገሮች ነው ውጤታማ መሆኑን የሚነገረው፡፡የተማከለ ስልጣን ስለሚከተል ደግሞ ወደ አምባገነንነትና ፈላጭቆራጭነት የሚያመራ የመንግስት አወቃቀር ነው፡፡ለነ እንጂኔር ይልቃል ግን ይህ ጉዳይ ወሳኝ ነው፤ ህዝቡን እንደፈለጉ ለመርገጥ በር የሚከፍት ነውና፡፡ስለሆነም ነው ወደ አሃዳዊ ስርዓት የሚመልስ ህገ ይልቃሎች የቀረፁት፡፡

ከቡድን መብት ይልቅ የግለሰብ መብቶች?

ከቡድን መብት ይልቅ የግለሰብ መብት የሚያስቀድሙት ክላሲካል ሊበርታርያኖች ነበሩ፡፡ቡድን የግለሰቦች ስብስብ ሰለሆነ የግለሰቦች መብት ከተከበረ የቡድኑም ይከበራል በማለት ይከራከራሉ፡፡አሁን ግን ጊዜው ተቀይሯል፤የቡድንና የግለሰብ መብቶች እኩል መካተት አለባቸው፡፡የሰው ልጅ በተፈጥረው ማህበራዊ ነው፤ በማህበር ይኖራል፡፡በማህበር ሲኖር ለማህበሩ የሚመቹ ባህሎች፣ ቋንቋዎች፣ ልምዶችና እምነቶችን ያዳብራል፡፡እነዚህ ነገሮች ከተነኩበት ወይም በነፃነት እንዲያከናውን ከተከለከለ ማመፁ አይቀርም፡፡ስለሆነም ከግለሰብ መብቶች በተጨማሪ የቡድን መብቶችም ሊከበሩለት ይገባል፡፡
የእኛ ሃገር ተቃዋሚዎች በተለይም ሰማያዊ ፓርቲ ግን የግለሰብ መብት የቡድን መብትን መቅደም አለበት ባያች ናቸው፡፡ይህ ዓይነት አካሄድ ግን ከጥቅሙ ጉዳቱ እንደሚያመዝን ከታሪክ መማር እንችላለን፡፡የሃገራችን ህዝቦች ከአማርኛ በስተቀር በቋንቋቸው እንዲማሩና እንዲፅፉ አይፈቀድላቸውም ነበር፡፡በመሆኑም ባህላቸው ወደ መጥፋት ተቃርቦ ነበር(ከሞቱ ቋንቋዎች የጠፋም ይኖራል)፡፡  

ከብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሉዓላዊነት ይልቅ የሕዝቦች ሉዓላዊነት?

የኢፌዴሪ ህገ መንግስት የብሔር፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሉዓላዊነት ካስፈለገም እስከ መገንጠል ድረስ ይፈቅዳል፡፡አብዛኞቹ የሃገራችን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ይህ መብት የሚፈቅደው አንቀፅ(39) አምርረው ሲኮንኑ መታዘብ የተለመደ ነው፡፡ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ወደዱም ጠሉም በአንድነት ስም ተረግጠው መኖር አለባቸው ማለት ነው፡፡ከማስገደድ ግን በመፈቃቀድ አብሮ መኖር አይሻልም? ስምምነት ከሌለ ማንኛውም ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ነፃነታቸው ለማስከበር የሚስቆማቸው ሃይል ይኖራል ብሎ ማመን ሞኝነት ነው፡፡ሰማያዊ ፓርቲ ድግሞ አንቀፅ 39ን የሚሽር የግሌ ህገ መንግስት አለኝ እያልን ነው፡፡ሰማያዊ ፓርቲ የስልጣን ባለቤት ከሆነ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሉዓላዊነት ብሎ ነገር አይኖርም፡፡በህዝቦች ሉዓለላዊነት ስም ይደፈጠጣል፡፡
እናም ሰማያዊ ፓርቲ ከፌዴራላዊ የመንግሥት አወቃቀር ይልቅ አሀዳዊ የመንግሥት አወቃቀር፣ከቡድን መብት ይልቅ የግለሰብ መብቶች፣ከብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሉዓላዊነት ይልቅ የሕዝቦች ሉዓላዊነት እንዲሁም መሬት ከመንግስት ባለቤትነት ይልቅ የግለሰቦች እንዲሆን የሚያደርግ ህገመንግስት አርቅቋል፡፡ከመሬት ባለቤትነት በስተቀር ግን ሌሎቹ ለዘመናት ተመኩረው ያልተሳኩ ናቸው፡፡ስለሆነም ወደ ኋላ መመለሱ አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡