Ø ‹‹በኢትዮጵያ ውስጥ በእንዲህ ዓይነት ስፋት ድርቅ ተከስቶ አያውቅም››
Ø ‹‹ከአየር ንብረቱ መዛባት ጋር ተያይዞ ብዙ ቦታዎች ላይ ያሉ ግድቦቻችን በከፍተኛ ደረጃ ቀንሰዋል፡፡››
Ø‹‹ስለዚህ ድርቁ ራሱ በፈጠረው የውኃ ችግር የኤሌክትሪክ እጥረት አጋጥሟል፡፡››
Ø‹‹በድርቁ የተጠቃው የህዝብ ብዛት እየተጠና ነው፤ ‹‹አሥራ አምስት ሚሊዮንም ሊሆን ይችላል፤ ሃያ ሚሊዮን ሊሆን ይችላል፡፡››
Ø ‹‹መጀመሪያዎቹ አካባቢ ከውጭ ያስገባነው ወደ 250 ሺሕ ሜትሪክ ቶን እህል ነበር፡፡ አሁን ግን ተጨማሪ 650 ሺሕ ሜትሪክ ቶን እህል እንደገና አዘናል፡፡››
Ø ‹‹የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ገና ተግባራዊ አልሆነም፡፡ አዲስ አበባ የራሷ ድንበር አላት፡፡ ከድንበሩ አንድ ኢንች ወደ ኦሮሚያ አትገባም፡፡››
ጠቅላይ
ሚኒስትር ኃይለ ማርያም
ደሳለኝ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከሪፖርተር ጋርባደረጉት ረዘም ያለ ቃለ መጠይቅ ድርቁ ያስከተላቸው መጠነ ሰፊ ችግሮችን ይፋ አድርጓል፡፡ጠቅላይ ሚኒትሩ ባሃገራችን ከሚገኙ
የግል መገናኛ ብዙሐን ቃለ መጠይቅ ሲያደርጉ የመጀመርያቸው ሲሆን በኢትዮጵያ የተከሰተው እጅግ አደገኛ ድርቅ የሃገሪቱ አንድ
አራተኛ የሚሆነውን ህዝብ ለተረጅነት ሊዳርግ እንደሚችልና የግድቦች የውሃ መጠን በጣም በመቀነሱ ምክንያት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ
ዕጥረት ማስከተሉን ተናግሯል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዘንድሮ የተከሰተው ድርቅ ‹‹በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከተከሰተው ድርቅ ሰፋ ያለና›› አብዛኛው የሃገሪቱ ክፍል
ያካለለ በመሆኑ የተረጂዎች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል ገልፀዋል፡፡‹‹ማንም የማይቆጣጠረው ሰፊ አካባቢ በድርቁ ተጠቅቷል፡፡›› ያሉት ሚኒስትሩ ‹‹ቁጥሩ ምን ይሁን ምን በሒደት የሚወሰን ነው፡፡ አሥራ አምስት ሚሊዮንም ሊሆን ይችላል፤ ሃያ ሚሊዮን ሊሆን ይችላል፡፡ እኛ ብዙ ትኩረት የምንሰጠው ቁጥሩ ላይ አይደለም፡፡ ዋናው ግን እኛ እያደረግን ያለነው እያንዳንዱ ቤተሰብ ምን ደረጃ ላይ ነው? የሚለው ነው›› ሲሉም አስተያየታቸውን
አክሏል፡፡