Sunday, November 29, 2015

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በድርቁ የተጠቃው የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት ‹‹20 ሚሊዮን ሊሆን ይችላል›› አሉ


Ø  ‹‹በኢትዮጵያ ውስጥ በእንዲህ ዓይነት ስፋት ድርቅ ተከስቶ አያውቅም››

Ø  ‹‹ከአየር ንብረቱ መዛባት ጋር ተያይዞ ብዙ ቦታዎች ላይ ያሉ ግድቦቻችን በከፍተኛ ደረጃ ቀንሰዋል፡፡››

  Ø‹‹ስለዚህ ድርቁ ራሱ በፈጠረው የውኃ ችግር የኤሌክትሪክ እጥረት አጋጥሟል፡፡››

Ø‹‹በድርቁ የተጠቃው የህዝብ ብዛት እየተጠና ነው፤ ‹‹አሥራ አምስት ሚሊዮንም ሊሆን ይችላል፤ ሃያ ሚሊዮን ሊሆን ይችላል፡፡››

Ø  ‹‹መጀመሪያዎቹ አካባቢ ከውጭ ያስገባነው ወደ 250 ሺሕ ሜትሪክ ቶን እህል ነበር፡፡ አሁን ግን ተጨማሪ 650 ሺሕ ሜትሪክ ቶን እህል እንደገና አዘናል፡፡››

Ø  ‹‹የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ገና ተግባራዊ አልሆነም፡፡ አዲስ አበባ የራሷ ድንበር አላት፡፡ ከድንበሩ አንድ ኢንች ወደ ኦሮሚያ አትገባም፡፡››

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ


ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከሪፖርተር ጋርባደረጉት ረዘም ያለ ቃለ መጠይቅ ድርቁ ያስከተላቸው መጠነ ሰፊ ችግሮችን ይፋ አድርጓል፡፡ጠቅላይ ሚኒትሩ ባሃገራችን ከሚገኙ የግል መገናኛ ብዙሐን ቃለ መጠይቅ ሲያደርጉ የመጀመርያቸው ሲሆን በኢትዮጵያ የተከሰተው እጅግ አደገኛ ድርቅ የሃገሪቱ አንድ አራተኛ የሚሆነውን ህዝብ ለተረጅነት ሊዳርግ እንደሚችልና የግድቦች የውሃ መጠን በጣም በመቀነሱ ምክንያት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ዕጥረት ማስከተሉን ተናግሯል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዘንድሮ የተከሰተው ድርቅ ‹‹በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከተከሰተው ድርቅ ሰፋ ያለና›› አብዛኛው የሃገሪቱ ክፍል ያካለለ በመሆኑ የተረጂዎች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል ገልፀዋል፡፡‹‹ማንም የማይቆጣጠረው ሰፊ አካባቢ በድርቁ ተጠቅቷል፡፡›› ያሉት ሚኒስትሩ ‹‹ቁጥሩ ምን ይሁን ምን በሒደት የሚወሰን ነው፡፡ አሥራ አምስት ሚሊዮንም ሊሆን ይችላል፤ ሃያ ሚሊዮን ሊሆን ይችላል፡፡ እኛ ብዙ ትኩረት የምንሰጠው ቁጥሩ ላይ አይደለም፡፡ ዋናው ግን እኛ እያደረግን ያለነው እያንዳንዱ ቤተሰብ ምን ደረጃ ላይ ነው? የሚለው ነው›› ሲሉም አስተያየታቸውን አክሏል፡፡

‹‹ሌብነት የለመደ በአንድ ሳምንት ውስጥ ቴሌቪዥን ላይ ወጥተን ስለጮህን እጁን ይሰበስባል ማለት አይደለም›› ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ


ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲህ ዓይነት ቆይታ ከግል የኅትመት ሚዲያ ጋር ሲያደርጉ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቆይታቸውም ወቅታዊ በሆኑ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በቅርቡ ከተከሰተው ድርቅ አንስቶ ስለመልካም አስተዳደር ችግሮች፣ እንዲሁም በኤርትራ ጉዳይ ላይ ያደረጉት ልዩ ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡  
ሪፖርተር፡- ከኤልኒኖ ጋር በተያያዘ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ድርቅ መከሰቱ ይታወቃል፡፡ እስካሁን ድረስ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር 8.2 ሚሊዮን መድረሱን መንግሥት አስታውቆ ነበር፡፡ ሆኖም ግን ዓለም አቀፍ የዕርዳታ ድርጅቶች የተረጂዎቹ ቁጥር 15 ሚሊዮን እንደሚደርስ እየተናገሩ ነው፡፡ በተጓዳኝ ደግሞ ከለጋሾች የሚጠበቀው ዕርዳታ በተጠበቀው መጠን እየተገኘ አይደለም፡፡ ስለዚህ ነገሮች በዚሁ ከቀጠሉ መንግሥት ጉዳዩን እንዴት ለመወጣት አስቧል? የሚታጠፉ የመንግሥት ፕሮጀክቶች አሉ ብለዋል፡፡ የትኞቹ ናቸው? የአገሪቱ የአደጋ መከላከል ዝግጁነት ምን ይመስላል? በተለይ ከዚህ ድርቅ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጥያቄ ተጎጂዎች ዕርዳታው በአግባቡ እየደረሳቸው አለመሆኑን ነው፡፡ እኛም በቦታ ላይ ተገኝተን ይህን መታዘብ ችለናል፡፡ ስለዚህ በድርቁ የተጎዱ ወገኖችን የመርዳቱ ሒደት ቅንጅት የጎደለው ነው ይባላል? እዚህ ላይ ምን ይላሉ?

Tuesday, September 1, 2015

አእምሮ የሌለው ሕዝብ…( ነጋድራሰ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ፣ ስራዎች)




የባለ ምጥቁ አእምሮአርቆ አሳቢእጅግ ታላቅ ሰው...የገብረ ሕይወት ባይዳኝ ስራዎችን እስካሁን ባለማንበቤ ምንኛ ቆጨኝ መሰላችሁ፡፡እስኪ፣ እርሳቸው ከፃፏቸው ያስገረሙኝን ቃል በቃል ላካፍላችሁእንደኔ ያላነበባችሁ ጓደኞቼ በእርግጠኝነት ትገረማላችሁ፡፡ እርሳቸው ይህን ከፃፉት አንድ መቶ ዓመታት( አንድ ክፍለ ዘመን) እንደ ጉድ እብስ ብሏል፡፡ያም ሆኖ ግን፣ የእርሳቸው ወርቃማ ምክሮች ዛሬም ድረስ ተግባራዊ ሆኗል ብየ ለመናገር ያስቸግረኛል፡፡
‹‹ምነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእንቅልፍህ መቸ ትነሳለህ? በዓለም ላይ የሚደረገውን ነገር ለማየትስ ዓይንሀን መቸ ትከፍታለህ?
አእምሮ በአእምሮ ካልሆነ በቀር በሌላ አትታገድም፡፡ስለዚህ ወዮለጽ በድንቁርና ለሚቀመጥ ሕዝብ ውሎ አድሮ ይደመሰሳልና፡፡››(ገፅ 22)
መንግስታችንም እንድትቀና የሚከተሉት አስር ነገሮች በቶሎ ቢፈፀሙ ማለፍያ ነበር፡፡
1.
ለመንግስት የሚሆን ገንዘብና ለንጉሱ የሚሆነውን ገንዘብ በስርዓት ይለይ
2.
ሕዝቡ ለመንግስት የሚከፍለው ግብር እንደየሀብቱ መጠን ቁጥር ሁኖ ይታወቅለት
3.
ሕዝቡም የሚከፍለው ግብር በብር እንጂ በእህል፣ በማርም በፍሪዳም አይሁን፡፡የመንግስት ስራ ሁሉም በባላገር አይሰራ፤ በባለ ደሞዝ እንጂ፡፡
4.
የአማርኛ ቋንቋ ገና ስዋስው አልተበጀለትም፡፡ ስለዚህ መንግስታችን ከያገሩ ስዋስው የሚያውቁትን ሊቃውንት ሰብስቦ ያማርኛን ቋንቋ ስዋስው ቢያስወጣ ደግ ነው፡፡
5.
ፍትሐ ነገስታችን ከዛሬው ያደባባይ ስርዓት ጋር አይስማማም፡፡ስለዚህ መንግስት የስርዓት አዋቂዎችን ሰብስቦ ከኤሮጳ ስርዓት ጋር የተስማማ ፍትሐ ነገስት ያውጣ፡፡የተፃፈ ስርዓት የሌለው መንግስት ብዙ ዕድሜ የለውም፡፡
6.
ያገራችን ሰራዊት ስርዓት የለውም፡፡ ስለዚህ የኤሮጳን መኳንንት አምጥተው ሰልፍን ቢማር ማለፍያ ነበር፡፡
7.
የዛሬው የመንግስታችን ብር የተበላሸ ና፡፡ ስርዓት ውል የለውም፡፡ባንዱም አውራጃ በጨው በሌላው በጥይት የሰፈራል፡፡
8.
ላገራችን ነጋዴ ስርዓት እስኪወጣለት ድረስ መንግስታችን አይቀናም፡፡
9.
ሕዝቡ ባንድ መንግስት ውስጥ መሆኑን አጥብቆ እንዲያውቀው አገሩን የሚዞሩ ተቆጣጣሪዎች ይሸሙበት፡፡
10.
የሃይማኖት አርነት ይታወጅ፡፡የሃይማኖት አርነት ጥቅም መሆኑን የማያውቅ ብዙ ሰው ይኖራል፡፡ያገራችን ሰው የተዋህዶ ሃይማኖት ከሁሉ ሃይማኖት ይበልጣል ብሎ ያምናል፡፡ በልጦ ግን ምን ረባን? ማንስ አወቀው? …ደግሞም ባገራችን አንድ የድንቁርና ነገር አለ፡፡ ሃይማኖቱ ተዋህዶ ያልሆነ ሰው አንደ ርኩስ ይቆጠራል፡፡ይህም እጅግ ያስቃል፡፡ አእምሮ የሌለው ሕዝብ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ሳያውቅ የእግዚአብሔር ጠበቃ ሊሆን ይወዳል፡፡
ሃይማኖት የልብ ነገር ነው፡፡ስለዚህ ሰማያዊው ንጉስ እንጂ የዚህ ዓለም ንጉስ አይቆጣጠረውም፡፡(ገፅ 23-28)
በአጠቃላይ፣ አእመሮ የሌለው ሕዝብ የሚከተሉትን ወሳኝ ነገሮች አይኖሩትም፡፡