…ከ37 ዓመታት በፊት መስከረም 1969 ዓ.ም ኢህአፓ በአንባገነናዊው የደርግ መሪ መንግስቱ
ሃይለማርያም ላይ የግድያ ሙከራ አድርጓል፡፡ያኔ ሂወት ተፈራ እና ገታቸው ማሩ ከኢህአፓ አባልነታቸውም ባሻገር በጣም የሚዋደዱ የቁርጥ
ቀን ፍቅረኞች ነበሩ፡፡ጌታቸው ማሩ ‹‹የታዎር ኢን ዘ ስካይ›› ዋና ገፀ ባህሪ ሲሆን በወቅቱ የአብዮት መስራች፣ ኋላም የኢህአፓ
የፖሊት ቢሮ አባልና የወጣቶች ሊግ አስተባባሪ ነበር፡፡ እናም ሂወት ‹‹ በመንግስቱ ላይ ስለ ተፈፀመው የግድያ ሙከራ ምን ታስባለህ?››
በማለት ጌታቸውን ትጠይቀዋለች፡፡
የጌታቸው መልስ ‹‹ መግለፅ ከምችለው በላይ ቅጥ ያጣ እብደት ነበር፡፡የሃገር መሪን ለመግደል
መሞከር መፈንቅለ መንግስት ሲሆን ግለ ሰቦችን መግደል ደሞ ከግበረ ሽበራ ተግባር ይቆጠራል፡፡እንደኛዎቹ ዓይነት ፓርቲዎች በዚሁ
ተግባር መሳተፍ የለባቸውም፡፡የከተማው የትጥቅ ትግል ሐሳብ ፓርቲው ይዞት ከተነሳው አቅጣጫ ያፈነገጠ ነው፡፡ ፓርቲው በጥፋት መንገድ
ላይ እየተራመደ ይገኛል…›› የሚል ነበር፡፡ወቅቱ የስልሳዎቹ አብዮት ሙሉ በሙሉ ተቀጣጥሎ የሚንቀለቀልበት የዕብደት ጊዜ ነበርና
የእነ ጌታቸው ማሩ ጥልቅና ዘመን ተሻጋሪ እይታ ማንም ሊረዳው አልቻለም ነበር፡፡ጌታቸው ተቀባይነት አላገኘም…እናም በአንጃነት ተፈርጆ
ተገደለ፡፡ሆኖም ግን የጌታቸው ማሩ ግድያ የግለ ሰብ ግድያ አልነበረም…የሃገርና የትውልድ ግድያ እንጂ፡፡

