የገጣምያን ወግ


ወይ ጊዜ



አንዱን እየጣለ ሌላውን ሊያነሳ
የመጣውን ሊያነግስ ነባሩን ሊያስረሳ
ጊዜ ፈጣን ባቡር ሄደ እየከነፈ
በየፌርማታው ላይ ሰው እያራገፈ፡፡

ምንጭ፡
አንዱዓለም ኪዳኔ፡፡2002 ዓ. ም፡፡በዝናብ ቅጠሪኝ ፡፡(3ኛ ዕትም)፡፡አዲሰ አበባ፡፡

No comments:

Post a Comment