| ቢዛ ፊልም |
በሬድዮና ቴሌቪዥን ዝግጅቶች የምናውቀው ብርሃነ ንጉሰ ወደ ፊልም ኢንዲስትሪው በይፋ መቀላቀሉን የሚያበስር ወሬ ይዞ
ብቅ ብሏል፤ቢዛ ፊልም፡፡በፖስተሩ ላይ ያሉ ተዋናዮች ስመለከት የልጅነት ጀግኖቼን አስታወሱኝ፡፡እነ ሻምበል ሮማን፣ እነ ጓል ዓይነታ፣ እነ ሲሳይ ገበል፣ እነ ጉማ፣ እነ ቀጭ ሕርሙ፣ ሽላ መረብ…
በተላይ ያቺ ሰላም ተስፋይ የሚሏት ልጅ ሳይ በጣም ነው የደነገጥኩት፡፡ያቺ
ገና ህፃን እያለሁ ‹‹ማንጅስ፣ ይህ ትግል ከግቡ የምታደርሱት እናንተ ናችሁ፤ ስጋ ብፆት›› የሚል ትንቢት የነገረችኝ ሻምበል ሮማን
በአካል ድቅን አለችብኝ፡፡በህይወት ትኑር አትኑር አላውቅም፡፡ምስሏና አነጋገሯ ግን በህይወት እስካለሁ ድረስ ከእኔ ጋር ይኖራል፡፡ይህ
እውነታ የእነ እንትና ጭሆት ሊፈቀው አይችልም፡፡በጭራሽ!
እነ ሻምበል ሮማን የታገሉት የደርግ ስርዓት አሁን ባለው ስርዓት
ለመተካት እንዳልነበረ በእርግጠኝነት መመስከር እችላለሁ፡፡ለዛም ነው
‹‹ትግሉን ከግቡ የምታደርሱት እናንተ ናችሁ›› ያለችኝ፡፡በእቅፏ አድርጋ ስስ ፀጉሬን እያሻሸች፣ በራሽን መልክ ተሰጠቻት ዳቦ በሻይ
ለእኔ አስረክባ፡፡ይህ መሆኑን ሁለት ጠላቶች እንዳፈራ ግድ ብሎብኛል፡፡ባንድ በኩል ሁሉንም ጠቅልሎ ሲያበቃ፣ ሁሉንም እንድናጣ የደረገን
ስርዓት መታገል ይኖርብኛል፡፡በሌላ በኩል ደሞ ይህ ስርዓት ሙሉ በሙሉ የጠቀለለውን ሁሉ በሃይል ለመረከብና ‹‹የጠቅላይ አግላይ››
አዙሪቱን ለማጦዝ የተዘጋጁትን መፋለም እንዳለብኝ ያሳብቃል፡፡

