በኛ ሃገርስ መቼ ይሆን ጋዜጠኞች
አጭበርባሪ ፖለቲከኞችን እንዲሁ በበሳል ጥያቄዎችን አፋጥጠው በህዝብ ፊት ማስለቀስ የሚችሉት?
| Ryutaro Nonomura |
በኛ ሃገር ጋዜጠኞች ፖለቲከኞች
ፀሐይ እንዳይመታቸው ዣንጥላ ይዘው ወደ ሄዱበት ወድያ ወዲህ ሲሉ ነው የሚታወቁት፡፡ ይህ አስገራሚ ጃፓናዊ ፖለቲከኛ የህዝብ ገንዘብ
በምን መልኩ እንዳጠፋው በጋዜጠኞች ተጠይቆ መልስ መስጠት ሲያቅተው በፕረስ ኮንፈረስ ላይ የተሌቪዥን ካሚራዎች ወደ እርሱ አነጣጥረውበት
ሳለ እንዲህ እንደ ህፃን ልጅ ስቅስቅ ብሎ በማልቀስ ዓልም ጉድ አሰኝቷል፡፡
የጃፓን ጋዜጠኞች እንዲ ዓይነቶቹ
ልክስክስ ፖለቲከኞችን የህዝብ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ይንቀጠቅጣሉ፣ ያደፋንቃሉ፡፡ የኛ ሃገር ፖለቲከኞች ግን በግልባጩ ጋዜጠኞችን
በጥያቄ ሲያፋጥጡ፣ ሲያንቀጠቅጡ፣ሲያስለቅሱ ይስተዋላል፡፡ ዓንዶም ገብረየሱስ የሃገራችን ጋዜጠኝነት በደምብ ገልፆታል፤ እንደሚከተለው፡፡
ፖለቲከኛ እንዲህ ሲነፋረቅ
ማየት እንዴት ያስደስታል? ‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› ነው ያለው መፅሐፉ? ለካ ህዝብ ሲያስለቅስ ለኖረው ፖለቲከኛም እንዲህ የሚያለቅስበት
ጊዜ አለ? እስኪ ሊንኩን በመጫን ፎቶውን ተመልከቱና እናንተም እንደኔው ተገረሙ፡፡
No comments:
Post a Comment