እውነቱ በእውነተኞች ሲፈርጥ
የዋሾዎች፣የምስጦች ድብቅ ሴራ
ሲጋለጥ
ከንቱነታቸው ዓይኖቹን ሲያፈጥ፣ጥርሶቹን
ሲያገጥ
የወገን ልብ ቅቤ ሲጠጣ፣በደስታ
ጩቤ ሲረግጥ
ያኔ! ያኔ ነው መዝለል፣ያኔ
ነው መደሰት
በልዩነት ተከባብሮ መኖር፤ለሃገራዊ አንድነት
በዋሾዎች፣በምስጦች፣በትዕቢተኞች፣በጨቋኞች፣በአስመሳዮች
ላይ
በድህነት፣በኋላ ቀርነት፣በሙስና፣በመልካም
አስተዳደር እጦት ላይ
ቆፎው እንደተነካበት ንብ
ሆ! ብሎ በአንድነት መዝመት
ይህ ነው ያገር ፍቅር! ይህ
ነው ኢትዮጵያዊነት፡፡
ይህ ነው ታሪካችን
የኢትዮጵያዊነት መለያችን፡፡
እችን ግጥም መሳይ ለመቋጥ ያነሳሳህኝ ወገኔ መሳፍንትዘ ጎንደር ከታላቅ አክብሮት ጋር መስጋናየ ይድረስህ፡፡
No comments:
Post a Comment