Tuesday, August 27, 2013

ሁሉም 12ኛ ክፍል የላይበርያ ተማሪዎች የዘንድሮ የዩኒቨርሲቲ መግበያ ፈተና ወደቁ


አጠቃላይ በዛታቸው 25,000 የሚጠጋ የላይበርያ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባው ፈተና አንዳቸውም ሳያልፉ መቀርታቸውን የቢቢሲ ድረገ ገፅ ዘግበዋል።
 ተማሪዎቹ የትምህርት ፍላጎት እንደሚያንሳቸውና የእንግሊዝኛ ቋንቋ መስርታዊ እውቀት እንደሌላቸው አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር ተናግረዋል።

  የላይበርያ ትምህርት ሚኒስተርዋ ወይዘሮ ዴቪድ ታርፓ አንድ ተፈታኝ እንኳን የዩኒቨርሲቲ መግበያ ፈተናውን ማለፍ አለመቻሉን ለማመን መቸገራቸውን አስታውቀዋል። << የተምህርት ተቋሞች ብዙ ችግሮች እንዳሉባቸው አውቃለሁ፤ይሁን እንጂ ፈተናውን የወሰዱ ሁሉም ተማሪዎች ወድቀዋል ሲባል ግን ያጠራጥራል።ዘር ለማጥፋት ይሚደረግ ጅምላ ጭፍጨፋ ሊባል ይችላል>> በማለት ነው ሁኔታውን የገለፀት።ስለሆነም የተማሪዎቹ የፈተና ውጤት ማየት እንደሚፈልጉም አስታውቀዋል፤ወይዘሮ ዴቪድ።

ሞሞዱ ጌትዋህ የተባሉ የዩኒቨርሲቲ ቃለ አቀባይ በቦኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በውሳኔው እንደሚፀናና ስሜታዊነት ውሳንያችው እንደማያስቀይራችው ተናግረዋል።

**************************************************************************************
<<ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም>> አሉ አበው።አሁን ጉዱን ሰምተናል፤መስከረም ሆይ ተሎ ነይ።

No comments:

Post a Comment